Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin
  • Home
  • Notice
  • About us
    • Staff
    • Holidays
  • Visit Ethiopia
    • Geography
    • Population
    • History
    • Climate
    • Calendar
  • Consular Services
    • Diaspora and Consular Affairs Section
    • የቆንስላ አገልግሎት
    • በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚከሰት ወሳኝ ኩነት መመዝገብ
    • Consular
    • Further Services
    • Konsularische Dienstleistungen
    • Visa
  • Contact
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አስረኛ አመት ግንባታን በማስመልከት የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ

Breaking News/ News/ Uncategorized

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አስረኛ አመት ግንባታን በማስመልከት የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ

Public Diplomacy Apr 7, 2021

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አስረኛ አመት ግንባታን በማስመልከት የኢፌዴሪ ሚሲዮኖች፣ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሳተፉበት የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ፡፡

ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት ባስተላለፉት መልዕክት ዳያስፖራውን በሚገባ ካስተባበርነውና ተሳትፎውን እንዲያሳድግ ከረዳነው ሃገርን የሚቀይር ዕምቅ አቅም እንዳለው የሃገራትን ተሞክሮ በመጥቀስ አስረድተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም ዳያስፖራው ሃብት ለማሰባሰብና የኢትዮጵያን ፍትሐዊ ተጠቃሚነት መርህን ለዓለም ለማስገንዘብ እያደረገ ላለው የፐብሊክ ዲፕማሲ ስራ ስጋናቸውን አቅርበው፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባባር ቦንድ መሸጥ ለማይቻልባቸው አካባቢዎች አማራጭ የሃብት ማሰባሰቢያ መንገድ መቀየሱን ጠቅሰዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ም/ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሄም በበኩላቸው ኢትዮጵያውያን ግድቡን በራሳቸው አቅም ጀምረው ለዚህ ደረጃ በማብቃታቸው ኩራት ሊሰማቸው እንደሚገባ ገልጸው፣ ቀሪ ስራዎችም ከፍተኛ ሃብትና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራ የሚጠይቁ መሆናቸውን ታሳቢ በማድረግ ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡በመድረኩ ላይ ለውይይት መነሻ የሚሆን ጽሑፍ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ም/ቤት ጽ/ቤት በኩል ቀርቧል፡፡በውይይቱ ተሳታፊ የነበሩ ክቡራን አምባሳደሮችና የሚሲዮን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሃብት አሰባሰብ አንጻር የሚታዩ ደካማ ጎኖቹ በሚጠናከሩበትና አዳዲስ አሰራሮች በሚፈጠሩበት፣ ያሉ ጥንካሬዎችም ጎልብተው መሄድ በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳብና አስተያየቶችን አንስተው ከመድረክ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

Related Posts

H.E. Ambassador Mulu discusses with Honorable Katrin Langensiepen

Breaking News /

H.E. Ambassador Mulu discusses with Honorable Katrin Langensiepen

ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany

News /

ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany

የክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ብዙነህ፣  የኢትየጵያ ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በጀርመን  ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር እና ልዩ መልክተኛ የ2015 አዲስ ዓመት መልካም ምኞት መልዕክት

Uncategorized /

የክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ብዙነህ፣ የኢትየጵያ ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በጀርመን ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር እና ልዩ መልክተኛ የ2015 አዲስ ዓመት መልካም ምኞት መልዕክት

‹ H.E. Ambassador Mulu Solomon and Ms Nicol Adamcova, Director of the Sub-Saharan Africa Department at the Ministry of Foreign Affairs of Czech Republic holds Discussion › H.E. Ambassador Mulu holds talks with IGAD Ambassadors, Political Foundation Fellows and other Ambassadors

Visa , passport and ID request Link

Use the following link to obtain service without a Diplomatic visa.

Apply for a Visa Online:  http://www.evisa.gov.et/

Apply for Passport & Ethiopian-Origin ID Card online:  http://www.digitalinvea.com/

Latest Post

  • ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany
  • ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ / vacancy announcement
  • 17ተኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል (የኢትዮጵያዊነት ቀን) ቀን በበርሊን ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ተከበረ
  • Speech of Ambassador Mulu Solomon Bezuneh, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary and Special Envoy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to Germany, Czech Republic, Republic of Poland, Slovak Republic and designate to Ukraine, + othe

Improtanat Consular Contacts

በሚሲዮን ለሚሰጡ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከተሉትን የስልክ ቁጥሮች መጠቀም ይቻላል፡፡

  1. በርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ የስልክ ኦፕሬተር ቁጥር +4930772060

የቆንስላ ጉዳዮችን በሚመለከት ለሚሰጡ አገልግሎቶች

  1. ሰነድ አልባ ፣ፓስፖርት ፣ ፓስፖርት ይፈለግልኝ ፣ የትውልድ መታወቂያ

          ሀ. አቶ አሻግሬ ሀብታሙ +4915218016085

           ለ. ወ/ሮ ሽኩሪያ ዴታሞ  +49307720612

  1. ሰነድ ማረጋገጥ ፣ውክልና ፣ ወሳኝኩነት ማለትም /ጋብቻ/ ፣ ሊሴፓሴ ፣ ወደ አገር ቤት ለሚሄዱ የድጋፍ ደብዳቤዎች መስጠት ፣ ወደ አገር ቤት ለሚላክ አስከሬን የድጋፍ ደብዳቤ መስጠት

            አቶ ተክላይ መዝገበ +493077206142

           Email: teklay.mezgebu@mfa.gov.et

  1. ዲያስፖራ አካውንት መክፈት ፣ሞርጌጅ /በብድር ቤት መግዛት/ ፣ የቦንድ ሽያጭን በተመለከተ ፣ ወደ አገር ጠቅልለው ለሚገቡ የድጋፍ ደብዳቤ መስጠት ፣ የኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ኮሚኒቲ ማደራጀት ፣ ኢንቨስትመትን በተመለከተ /ኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሆኑ/

             ወ/ሮ ሰብለ ቱሉ +49307720615

             Email:  seble.dadi@mfa.gov.et

  1. በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎች

           +49307720616

Facebook

Ethiopian Embassy in Germany

Twitter

Follow @ethioingermany

Back to Top

Consular Service

Monday, Tuesday and Thursday
Morning 8:30 -12:30
Afternoon 13:30 – 17:30

The Embassy remains closed on German and Ethiopian holidays.

Working Hours:

Monday to Friday.
08:30 to 12:30 and 13:30 to 17:30

Address

Boothstrasse 20a, 12207 Berlin, Germany

  • About us
© Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin 2023