Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin
  • Home
  • Notice
  • About us
    • Staff
    • Holidays
  • Visit Ethiopia
    • Geography
    • Population
    • History
    • Climate
    • Calendar
  • Consular Services
    • Diaspora and Consular Affairs Section
    • የቆንስላ አገልግሎት
    • በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚከሰት ወሳኝ ኩነት መመዝገብ
    • Consular
    • Further Services
    • Konsularische Dienstleistungen
    • Visa
  • Contact

የኢትዮ-ቼክ ኮሚኒቲ ማህበር በይፋ ሥራ መጀመሩ ተገለፀ

Sep 14, 2022

ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን በጀርመን ፌደራላዊ ሪፓብሊክ፣ ቼክ ሪፓብሊክ ፣ፖላንድ ሪፓብሊክ ፣ስሎቫክ ሪፓብሊክ እና ዩክሬን የኢትዮጵያ.ፌ.ዲ.ሪ  ልዩ መልዕክተኛ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር  በክብር እንግድነት   በቼክ ዋና ከተማ በፕራግ በመገኘት የኢትዮ- ቼክ ማህበር መቋቋሙን በይፋ አበሠሩ ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ማህበሩ የተቋቋመው ኢትዮጵያን ለመርዳት በሚደረገው ጥረት  የራሳቸውን ከፍተኛ ሚና ለመወጣት እና እርስ በእርስ ለመረዳዳት ፈቃደኛ በሆኑ የዲያስፖራ አባላት በመሆኑ አድንቀዋል፡፡ ማህበሩ ጠንካራ ራዕይ ይዞ የተነሣ በመሆኑ ከምንግዜውም በላይ በልዩ ልዩ ሙያ የተሠማሩ የዲያስፖራ አባላትን ይዟል ፡፡ ለምሳሌ፡ የህክምና ዶክተሮች፣ የኢንፎርሜሽን  ኮሚዩኒኬሽን  ባለሙያዎች እና ተማሪዎችን ጭምር አካቷል።
አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ባደረጉት ንግግር የማህበር አባል መሆን ለመጠቀም ብቻ ሣይሆን ለመጥቀምና ለመሰጠት መሆን እንዳለበት ገልፀው ጊዜን፣ ገንዘብን፣ እውቀትን ለማህበረሰብ ግልጋሎት መስጠት ፣ በገንዘብ የማይተመን እርካታ ስለሚሰጥ በሙያ ፣በገንዘብ ፣ በልዩ ልዩ አቅም አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ፣ ማህበሩን ያልተቀላቀሉ ካሉ አንዲቀላቀሉ እና  አባል የሆኑ ያለጥቅም ሀገርንና ወገንን ለመርዳት በቁርጠኝነት በመስራት ምሣሌ እንዲሆኑ አሳስበዋል ።

በእለቱ ከተስበስቡት አባላት፣ የቆንስላ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ እና ለህዳሴ ግድብ ቦንድ ለመግዛት የሚፈልጉ ተመዝግበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ ዓመት የተስፋ ስሜትን እና ደስታን የሚቀሰቅሱ ሙዚቃዎች ቀርበዋል ።

የማህበሩ መስራች እና ፕሬዝደንት አቶ ተሻለ ሽበሽ በበአሉ ላይ ባደረጉት ንግግር በቼክ ሪፐብሊክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተጠናከረ ህጋዊ የሆነ ኢትዮ-ቼክ ኮሚኒቲ ማህበር በማቋቋም ጷጉሜ 5  ቀን 2014 ዓ.ም. ማህበሩ በይፋ ስራ መጀመሩን እና የአድነትን ቀን በአልን ደርበው ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ብዙነህ በተገኙበት ማክበሩን በደስታ ገልፀዋል፡፡

ቀጥለው መንግስት የያዘው የዜጋ ተኮር ፖሊሲ አድንቀው ፣ ቀድሞ ከተለመደው ውጭ ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞን ወደ ኮሚኒቲው ወርደው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እርስበር መተባበራቸውን እንዲያጠናክሩ እያደርጉ ያለውን የማበረታታት ተግባር አድንቀዋል።
በመቀጠል ኢትዮ-ቼክ ኮሚኒቲ ማህበር የተመሰረተበትን ምክንያት ሲያስረዱ፣ በቼክ ሪፕብሊክ እና በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮ- ቼካዊያን ማህበር ሣይኖራቸው ለበርካታ አመታት በግለሰቦች ፈቃድ ለዓመት በዓላት ሲገነኙ መቆየታቸውን ጠቅሰው፣  ነገር ግን በመደራጀት የተሻለ ሥራ መስራት ስለሚቻል በጋራ አቅምን እጎክብቶ ተሠሚነት ለማግኘትና የኮሚኒቲውን መብት ለማስከበር፣ እንዲሁም የማህበረሰባችንን ችግሮች በጋራ ለመፍታትና ለመቋቋም ፣ ድንቅ የሆኑ የጋራ ባህላዊ እሴቶቻችንን ለመጠበቅ እና ለማስተዋወቅ ፣ ከምንኖርበት ሀገር ባህል ህግና የኑሮ ዘይቤ ጋር በማጣጣም ውጤታማ እንድንሆን በሁለንተናዊ መልኩ የሚያግዝ፣ ከማንኛውም የዘር፣የፖለቲካና የሐይማኖት አመለካከት ልዩነቶች ነፃ የሆነ ጠንካራ ማህበር እንዲኖረን እራሳችንንና ሀገራችንን ለመርዳት ባለንበት ሀገር የተከበርን ዜጋ ለመሆን በመፈለግና እንዲሁም የእርስ በርስ የመቀራረብ፣ የመግባባት፣ የመረዳዳትና የመተጋገዝ ባህላችንን በማዳበር የተለያዩ ድጋፎችንም ለወገን  መስጠት እንድንችል በማሰብ ሁሉን አቀፍ የሆነ ኢትዮ-ቼክ ኮሚኒቲ ማህበር በሚል ስያሜ በእ.ኤ.አ. 15.07.2022 ማህበር  በማቋቋም ዛሬ ማህበሩ ስራ መጀመሩን በይፋ በመገለፁ፣ ደሥታቸውን ገልፀዋል።
በመጨረሻም ‘”ሁሉም የሚናፍቋት እናት ሃገራችን ያለችበት ሁኔታ የአደባባይ ሚስጥር በመሆኑ፣ ከምንግዜውም በተለየ ሁኔታ ዛሬ የልጆቿን ድጋፍ እና እርዳታ የምትፈልግበትም ወቅት በመሆኑ እኛ በቼክ ሪፕብሊክ ያለን ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን በሚገባ እንረዳለን፣ በሚያስፈልገው ሁሉ እና በዲጅታል ዘመቻው የIinternational community እያሳደረባት ያለውን ጫናንም በመከላከል ከጎኗ መሆናችንን ልናሳውቅ እንወዳለ”  ብለዋል።

 

Related Posts

ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany

News /

ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany

17ተኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል (የኢትዮጵያዊነት ቀን)  ቀን በበርሊን ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ተከበረ

News /

17ተኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል (የኢትዮጵያዊነት ቀን) ቀን በበርሊን ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ተከበረ

Speech of Ambassador Mulu Solomon Bezuneh, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary and Special Envoy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to Germany, Czech Republic, Republic of Poland, Slovak Republic and designate to Ukraine, + othe

News /

Speech of Ambassador Mulu Solomon Bezuneh, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary and Special Envoy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to Germany, Czech Republic, Republic of Poland, Slovak Republic and designate to Ukraine, + othe

‹ የአንድነት በዓል በኢትዮጵያ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ በርሊን ጳጉሜ 5 ቀን 2014 ዓ.ም በዙም ተከበረ። › ሀገራዊ የድጋፍ ጥሪ

Visa , passport and ID request Link

Use the following link to obtain service without a Diplomatic visa.

Apply for a Visa Online:  http://www.evisa.gov.et/

Apply for Passport & Ethiopian-Origin ID Card online:  http://www.digitalinvea.com/

Latest Post

  • ኤምባሲው ሀሙስ ጥር 11 ቀን 2015 የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ዝግ መሆኑን እንገልጻለን / The Embassy is closed on Thursday, January 19, 2023, on the occasion of Ethiopian holiday, Epiphany
  • ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ / vacancy announcement
  • 17ተኛው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል (የኢትዮጵያዊነት ቀን) ቀን በበርሊን ኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ተከበረ
  • Speech of Ambassador Mulu Solomon Bezuneh, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary and Special Envoy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to Germany, Czech Republic, Republic of Poland, Slovak Republic and designate to Ukraine, + othe

Improtanat Consular Contacts

በሚሲዮን ለሚሰጡ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚከተሉትን የስልክ ቁጥሮች መጠቀም ይቻላል፡፡

  1. በርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ የስልክ ኦፕሬተር ቁጥር +4930772060

የቆንስላ ጉዳዮችን በሚመለከት ለሚሰጡ አገልግሎቶች

  1. ሰነድ አልባ ፣ፓስፖርት ፣ ፓስፖርት ይፈለግልኝ ፣ የትውልድ መታወቂያ

          ሀ. አቶ አሻግሬ ሀብታሙ +4915218016085

           ለ. ወ/ሮ ሽኩሪያ ዴታሞ  +49307720612

  1. ሰነድ ማረጋገጥ ፣ውክልና ፣ ወሳኝኩነት ማለትም /ጋብቻ/ ፣ ሊሴፓሴ ፣ ወደ አገር ቤት ለሚሄዱ የድጋፍ ደብዳቤዎች መስጠት ፣ ወደ አገር ቤት ለሚላክ አስከሬን የድጋፍ ደብዳቤ መስጠት

            አቶ ተክላይ መዝገበ +493077206142

           Email: teklay.mezgebu@mfa.gov.et

  1. ዲያስፖራ አካውንት መክፈት ፣ሞርጌጅ /በብድር ቤት መግዛት/ ፣ የቦንድ ሽያጭን በተመለከተ ፣ ወደ አገር ጠቅልለው ለሚገቡ የድጋፍ ደብዳቤ መስጠት ፣ የኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ኮሚኒቲ ማደራጀት ፣ ኢንቨስትመትን በተመለከተ /ኢትዮጵያውንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሆኑ/

             ወ/ሮ ሰብለ ቱሉ +49307720615

             Email:  seble.dadi@mfa.gov.et

  1. በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎች

           +49307720616

Facebook

Ethiopian Embassy in Germany

Twitter

Follow @ethioingermany

Back to Top

Consular Service

Monday, Tuesday and Thursday
Morning 8:30 -12:30
Afternoon 13:30 – 17:30

The Embassy remains closed on German and Ethiopian holidays.

Working Hours:

Monday to Friday.
08:30 to 12:30 and 13:30 to 17:30

Address

Boothstrasse 20a, 12207 Berlin, Germany

  • About us
© Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin 2023