Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin
  • Home
  • Notice
  • About us
    • Administration and Finance
    • Staff
    • Holidays
  • Visit Ethiopia
    • Geography
    • Population
    • History
    • Climate
    • Calendar
  • Consular Services
    • Diaspora and Consular Affairs Section
    • የቆንስላ አገልግሎት
    • በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚከሰት ወሳኝ ኩነት መመዝገብ
    • Consular
    • Further Services
    • Konsularische Dienstleistungen
    • Visa
  • Contact

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁርን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

Jul 28, 2022

ሐምሌ 18 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ: የኢፌዴሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር የሆኑትን ስቴፋን አሁርን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በነጋገሩበት ወቅት፤ ኢትዮጵያና ጀርመን ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ወዳጅ ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
ቀደም ሲልም የጀርመን መንግስት ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያንን አስመልክቶ የኢትዮጵያ መንግስት እየሰራቸው ላሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ስኬታማነት የበኩሉን እገዛ ሲያደርግ መቆየቱንም አስታውሰዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሀገሪቱ የተካሄደውን አዲስ የመንግስት ምስረታን ተከትሎ እንደአዲስ መዋቀሩንና በርካታ ሃላፊነቶች እንደተጣለበትም በሰፊው አብራርተዋል፡፡ ሃላፊነቱን ከመወጣት አኳያም በየዘርፉ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን፣ ፕሮግራሞችንና እቅዶችን ነድፎ ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
በተለይ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ አስተማማኝ ሰላምን በማስፈንና ልማትን በማፋጠን ረገድ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ልዩ ልዩ አደረጃጀቶች ያላቸውን ድርሻና ሚና ለማጎልበት ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛልም ብለዋል፡፡
በየዘርፉ አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ቢሆንም ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ከማስቻል አኳያ በርካታ ተግዳሮቶች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም እንደአገር ለሚደረገው ሁለንተናዊ ጥረት የጀርመን መንግስት ድጋፍ ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ጠይቀዋል፡፡
በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁር በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሴቶችን በማብቃት፣ ወጣቶች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሰፊው እንዲሰማሩ በማስቻል፣ ሴቶችና ወጣቶች ጨምሮ አደረጃጀቶች ለሀገር ሰላምና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ እየተሰራ መሆኑ፣ በጦርነቱ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች ከሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ ባሻገር የሳይኮ ሶሻል ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑ እንዲሁም መንግስት ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እያደረገ ያለውን ጥረት ከልብ አድንቀዋል፡፡ እንደአገር እየተካሄደ ያለውን የሪፎርም ስራም እንደሚደግፉት አስታውቀዋል፡፡
በቀጣይም በሰላም ግንባታ፣ ሴቶችን በማብቃት፣ ሰብዓዊ ድጋፎችን ተደራሽ በማድረግ፣ በታዳሽ ሀይል አቅርቦት በሌሎችም መስኮች ኢትዮጵያ ለምታከናውናቸው ተግባራት ውጤታማነት ጀርመን የበኩሏን ድጋፍ እንደምታደርግ እንዲሁም በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት እንደሚሰሩ አምባሳደር ስቴፋን አሁር ቃል ገብተዋል፡፡
ምንጭ፡-የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፌስ ቡክ ገፅ

Related Posts

H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck

News /

H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck

በርሊን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ተካሄደ፣

News /

በርሊን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ተካሄደ፣

Ethiopia Day Celebration

News /

Ethiopia Day Celebration

‹ የጋብቻ ማስታወቂያ › H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck

Visa , passport and ID request Link

Use the following link to obtain service without a Diplomatic visa.

Apply for a Visa Online:  http://www.evisa.gov.et/

Apply for Passport & Ethiopian-Origin ID Card online:  http://www.digitalinvea.com/

Latest Post

  • H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck
  • የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁርን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡
  • የጋብቻ ማስታወቂያ
  • በርሊን የሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል አድሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

Improtanat Consular Contacts

1) Mr. Aschalew Kebede in charge of Diaspora Affairs And Consular Service
(English and Amharic Speaking )

Tel +49 176 83343348
Email: – aschalew.kebede@mfa.gov.et

2) Mr. Belete Yimer
(Staff Volunteer, English and Amharic Speaking)

Tel.+49 1590 6620634

3) Mr. Ashagre Habtamu
(Staff   Volunteer, Amharic Speaking)

Tel.+49 1590 6628036

4) Mr. Getu Hailu
(Staff Volunteer, Amharic Speaking)

Tel.+49 176 70955372

Facebook

Ethiopian Embassy in Germany

Twitter

Follow @ethioingermany

Back to Top

Consular Service

Monday to Friday
Morning 08:30 to 12:30

The Embassy remains closed on German and Ethiopian holidays.

Working Hours:

Monday to Friday.
08:30 to 12:30 and 13:30 to 17:30

Address

Boothstrasse 20a, 12207 Berlin, Germany

  • About us
© Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin 2022