Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin
  • Home
  • Notice
  • About us
    • Administration and Finance
    • Staff
    • Holidays
  • Visit Ethiopia
    • Geography
    • Population
    • History
    • Climate
    • Calendar
  • Consular Services
    • Diaspora and Consular Affairs Section
    • የቆንስላ አገልግሎት
    • በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚከሰት ወሳኝ ኩነት መመዝገብ
    • Consular
    • Further Services
    • Konsularische Dienstleistungen
    • Visa
  • Contact

(ግንቦት 05 ቀን 2014 ዓ.ም) በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራው የልዑካን ቡድን በጀርመን ቆይታው ከጀርመን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች እና የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ጋር በሚሲዮኑ ጽ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ ውይይት አድርገዋል።

May 13, 2022

በወቅቱ ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከነባርና አዳዲስ የሚሲዮኑ ሰራተኞች ጋር ትውውቅ ያደረጉ ሲሆን በጀርመን የስራ ጉብኝት ስላደረጉበት አዲስ የሚሲዮን ጽ/ቤት ህንጻ ግንባታን በተመለከተ ከጀርመን መንግስት አካላት ጋር ስለነበረው ውጤታማ ውይይት ማብራርያ ሰጥተዋል።
ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ለሰራተኛው በሰጡት ምክረ-ሃሳብ አገራችን ባላት ውስን ኃብት ላይ ተመርኩዛ በምታደርገው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ አሁን የሚታየውን ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ቁመና ማየት የተቻለ መሆኑን በማንሳት የሚሲዮን ሰራተኞች ይህንን ከግምት በማስገባት የአገርን ክብር የመጠበቅና የአገር ጥቅምን የማስጠበቅ ድርብ ኃላፊነት ያለባቸው መሆኑን አስገንዝበዋል። በጋራ መንፈስ (Team Spirit) መስራት ያስፈልጋል ያሉት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ሙሉ ጊዜን ለዚሁ ትልቅ ኃላፊነት መስጠት አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ክብርት ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን በማጠቃለያቸው የዜጎችን መብት ከማስጠበቅ፣ ዳያስፖራ ለአገር ጥቅም እንዲቆም ከማድረግና ዜጎች ከዩክሬን እንዲወጡ ከማድረግ አንጻር ሚሲዮኑ ለሰራው ስራ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም ዳያስፖራውና ምሁራን በተለያየ ዘርፍ ለአገራቸው በCOVID-19፣ በታላቁ የህዳሴ ግድብ መዋጮ፣ ለገበታ ለሀገር፣ ለአገር ሉዓላዊነት የማስከበር እና የተለያዩ ድጋፎች ላደረገው እንቅስቃሴ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ ከዋናው መስርያ ቤት ለሚሲዮን ለሚያስፈልጉ የተለያዩ ጉዳዮች ድጋፎች በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸል።
በመጨረሻም ክብርት አምባሳደር ሙሉ ሰለሞንና የሚሲዮኑ ዲፕሎማቶችና ድጋፍ ሰራተኞች ስለተደረገላቸው ገለጻ ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ሙሉ አቅማቸውን አሟጠው በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።

Related Posts

H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck

News /

H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁርን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

News /

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁርን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

በርሊን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ተካሄደ፣

News /

በርሊን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ተካሄደ፣

‹ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ › Her Excellency Ambassador Mulu Solomon attends the Invitation of the Prime Minister of Czech Republic

Visa , passport and ID request Link

Use the following link to obtain service without a Diplomatic visa.

Apply for a Visa Online:  http://www.evisa.gov.et/

Apply for Passport & Ethiopian-Origin ID Card online:  http://www.digitalinvea.com/

Latest Post

  • H.E. Ambassador Mulu Solomon holds a courtesy meeting with Dr. Dr. Christian Buck
  • የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አሁርን በዛሬው ዕለት በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡
  • የጋብቻ ማስታወቂያ
  • በርሊን የሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢድ አል አድሐ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

Improtanat Consular Contacts

1) Mr. Aschalew Kebede in charge of Diaspora Affairs And Consular Service
(English and Amharic Speaking )

Tel +49 176 83343348
Email: – aschalew.kebede@mfa.gov.et

2) Mr. Belete Yimer
(Staff Volunteer, English and Amharic Speaking)

Tel.+49 1590 6620634

3) Mr. Ashagre Habtamu
(Staff   Volunteer, Amharic Speaking)

Tel.+49 1590 6628036

4) Mr. Getu Hailu
(Staff Volunteer, Amharic Speaking)

Tel.+49 176 70955372

Facebook

Ethiopian Embassy in Germany

Twitter

Follow @ethioingermany

Back to Top

Consular Service

Monday to Friday
Morning 08:30 to 12:30

The Embassy remains closed on German and Ethiopian holidays.

Working Hours:

Monday to Friday.
08:30 to 12:30 and 13:30 to 17:30

Address

Boothstrasse 20a, 12207 Berlin, Germany

  • About us
© Embassy of The Federal Democratic Republic of Ethiopia in Berlin 2022